.
የንባብ ሰዓት፣መጽሃፍትን ለተፈናቀሉ ኢትዮጵያዊያን የማድረስ ጥረት በምስል
ኢትዮጵያ ውስጥ ባለው ጦርነት እና ከዚያም ቀደም ብለው በነበሩ የተለያዩ ግጭቶች ምክንያት በሚሊየኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ከመኖሪያቸው ተፈናቅለዋል ።የተለያዩ ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ለእነዚህ ለእነዚህ ዜጎች ምግብ እና ጊዜያዊ መጠለያን የመሰሉ መሰራታዊ ድጋፎችን እያደረሱ ይገኛሉ ። ኢትዮጵያ ሪድስ የተሰኘ ተቋም ግን ለየት ባለ መልኩ በየመጠለያ ጣቢያዎች መጽሃፍትን እያሰራጨ ይገኛል።ቀጣዮቹ ምስሎች ለየት ያለውን መርሃ ግብር ይዘት በጥቂቱ ያሳያሉ።

5
ኢትዮጵያ ሪድስ ወላጆች ለልጆቻቸው የንባብን ባህል እንዲያጋሩ ያበረታታል / በአማራ ክልል አጣዬ ከተማ የተነሳ

6
የንባብ ሰዓት ፣ ሶማሌ ክልል -ባቢሌ

7
በሶማሌ ክልል ባቢሌ የሚገኘው ጣቢያ በምስል ያጌጡ መጽሃፍት ከተዳረሱባቸው ስፍራዎች አንዱ ነው

8
ህጻናት በንባብ ላይ ፣ በአማራ ክልል አጣዬ ከተማ የተነሳ