መፀዳዳት በመፀዳጃ ቤት፤ "ፑ ቱ ዘ ሉ”

Your browser doesn’t support HTML5

ኢትዮጵያ ውስጥ ከሃያ ሁለት ሚሊየን በላይ ሰው በየገላጣ ሜዳና በየመንገዱ ይፀዳዳል።
እንዲህ ዓይነቱ ጠባይ ለተቅማጥና ለሌሎችም ውኃ ወለድ ወረርሽኖች፣ ለምግብ መበከልና ለበዙ የጤና ቀውሶች እንደሚያጋልጥ የተባበሩት መንግሥታት የህፃናት መርጃ ድርጅት ያጠናው ጥናት ያመለክታል።

በተለይ ህፃናት የዚህ ችግር ዋና ተጋላጭና ተጠቂ መሆናቸውንየሚገልፀው ዩኒሴፍ መፀዳጃ ቤትን በአግባቡ መጠቀምና ንፅህናን መጠበቅን ለማበረታታት "መፀዳዳት በመፀዳጃ ቤት" የሚል ዘመቻ ጀምሯል።

በዩኒሴፍ-ኢትዮጵያ የ“ዋሽ” ኦፊሰር ነፃነት ካሳ ከአሜሪካ ድምፅ ጋር ተወያይተዋል። (ዝርዝሩን ከተያያዘው የቪድዮ ዘገባ ያገኛሉ።)