ሁለት የቀድሞ ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎች ክስ ተቋርጦ ተፈቱ

Your browser doesn’t support HTML5

የፍትሕ ሚኒስቴር ክስ በማቋረጡ የተፈቱት፣ የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን (በእንግሊዘኛ ምኅጻሩ ሜቴክ) የቀድሞ ዋና ዲሬክተር ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው እና የቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አብዲ ሞሐመድ ዑመር ናቸው፡፡ ከአምስት ዓመት በላይ በእስር የቆዩት ሁለቱ የቀድሞ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተፈተው ከቤተሰቦቻቸው ጋራ መገናኘታቸውንም ጠበቆቻቸው ለአሜሪካ ድምፅ አረጋግጠዋል፡፡