ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ከአደጋ ለመጠበቅ የአስቸኳይ ጊዜ ዓዋጅ መታወጁን የሚኒስትሮች ምክር ቤት አስታወቀ፡፡
አዲስ አበባ —
ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ከአደጋ ለመጠበቅ የአስቸኳይ ጊዜ ዓዋጅ መታወጁን የሚኒስትሮች ምክር ቤት አስታወቀ፡፡
ምክር ቤቱ አዋጅን ያወጀው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገሪቱ እየታዩ ያሉ ሁኔታዎችን መነሻ በማድረግ መሆኑን ማምሻውን በተነበበው መግለጫ አመልክቷል፡፡ ምን ያህል እንደሚቆይና ሌሎች ዝርዝር ሁኔታዎችን ግን በመግለጫው አልተካተቱም፡፡
በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የተካሄደውን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ሲከታተል የዋለው እስክንድር ፍሬው ተከታዩን ዘገባ ልኳል፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5
የአስቸኳይ ጊዜ ዓዋጅ መታወጁን የሚኒስትሮች ምክር ቤት አስታወቀ