እ.አ.አ በ2020 ቫይረሱን ከአለማችን ጨርሶ የማጥፋት አለም አቀፍ እቅድ በኢትዮጵያ ምን ያህል እንደተተገበረ በመገምገምና ለቀጣይ አመታትም ምን ላይ ትኩረት በመስጠት መሰራት እንዳለበት በመመካከር ነበር ቀኑ ታስቦ የዋለው።
ዋሽንግተን ዲሲ —
የፌደራል የኤች አይ ቪ መከላከያና መቆጣጠሪያ ፅ/ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ አለሙ አኖ በኢትዮጵያ የኤች አይ ቪ ስርጭትና መከላለልን በተመለከተ ካለፈው አመት ጋር በማነፃፀር የተሻለ ለውጥ እንደታየ ገልፀዋል።
የብሔራዊ የኤች አይ ቪ መቆጣጠሪያና መከላከያ ፅ/ቤት የእቅድ ክትትልና ግምገማ ኦፊሰር ዶ/ር አቻምየለህ አለባቸው በኢትዮጵያ በቫይረሱ የሚሞተው የሰው ቁጥር መቀነስ ከፍተኛ ቢሆንም አዳዲስ በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር በመቀነስ ዙሪያ አሁንም መስራት ይገባናል በማለት ይናገራሉ።
file-photo
ከመስታወት አራጋው ጋር ያደርረጉትን ቆይታ ከበታች ያለውን የድምፅ ምልክት በመጫን ያድምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5
አለም አቀፉ የኤች አይ ቪ ኤድስ ቀን ለሃያ ስምንተኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ተከብሮ ዋለ