ሕገ መንግሥቱን ጨምሮ የተለያዩ ህጎች እንዴት መሻሻል እንዳለባቸው የሚቀርቡ የመፍትሄ ሃሳቦች እንዲበረታቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ ታገሰ ጫፎ አሳስበዋል።
አዲስ አበባ —
የመረጃ ነፃነትና የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ በመሻሻል ሂደት ላይ ካሉ ሕግጋት አንዱ መሆኑን የጠቀሱት አፈጉባዔ ታገሰ በዚሁ ርዕሰ-ጉዳይ ላይ የተዘጋጀ መፅሐፍ መርቀዋል።
መፅሐፉን የፃፉት የፓርላማ አባል አቶ አማኑኤል አብርሃም የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታና ዳራ ያሉትን ለማካተት መሞከራቸውን ገልፀዋል።
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5
የመረጃ ነፃነት በኢትዮጵያ