ብሄራዊ የስፓርት ፌዴሬሺኖች እዉቀት ባላቸዉ ሰዎች መመራት አለባቸው

  • እስክንድር ፍሬው

ቃለ ምልልስ ከአትሌት ሃይሌ ገብረ ስላሴ ጋር

Your browser doesn’t support HTML5

ቃለ ምልልስ ከአትሌት ሃይሌ ገብረ ስላሴ ጋር


ዓለም አቀፉና ብሔራዊ የስፓርት ፌዴሬሽኖች በዘርፉ እዉቀት ባላቸዉ ሰዎች መመራት እንዳለባቸዉ የሁለት ጊዜ የኦሎምቲክስ የወርቅ ሜዳሊያና የሃያ ሰባት የዓለም ክብረ-ወሰኖች ባለቤት አትሌት ሃይሌ ገብረ ስላሴ ተናገረ። በኢትዮጵያም የስፓርት ፌዴሬሽንኖችን የሚመሩ ሰዎች የሚመረጡበት ሁኔታ ሊቀየር እንደሚገባ አሳስቧል።

ለዓለም አቀፉ የአትሌትክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር እየተደረገ ባለዉ የፕሬዚደንትነት ፉክክር ከቅርብ ጉዋደኛዉ የከፍታ ዝላይ ሻምፒዮና Sergei Bubka ይልቅ ብዙም ለማይቀርባቸዉ አሁን የብሪታኒያ የምክር ቤት አባል የቀድሞ የኦሎምፒክ ሻምፒዮና Lord Sabastian Coe ድጋፉን መሰጠቱንም ሃይሌ በምሳሌነት ጠቅሷል።