በጦርነቱ 3.2 ቢሊዮን ብር የሚገመት የውሀ መሰረተልማት መውደሙ ተገለፀ

Your browser doesn’t support HTML5

በጦርነቱ 3.2 ቢሊዮን ብር የሚገመት የውሀ መሰረተልማት መውደሙ ተገለፀ

በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት 3.2 ቢሊዮን ብር የሚገመት የውሀ መሰረተልማት መውደሙን የውሀ እና ኤነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ገለፁ፡፡

ከትግራይ እና ከአማራ ክልሎች ያነጋገርናቸው ነዋሪዎችም የውሀ ተቋማቱ በጦርነቱ በመውደማቸው ችግር መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

ተቋማቱን ለመጠገን የአጭር እና የረዥም ጊዜ ዕቅድ ተይዞ እየተሠራ መሆኑን ዶ/ር ሀብታሙ ገልፀዋል፡፡

አስተዳደራዊ መዋቅር ባለባቸው የአፋርና የአማራ ክልሎች ከውሀ ቢሮዎች ጋራ እየተሠራ እንደሆነ የተናገሩት ዶ/ር ሀብታሙ፣ በትግራይ ክልል ግን መዋቅሩ ስለሌለ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከማዕከል ባለሞያዎችን እየላከ የጥገና ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ዘገባ ያገኛሉ።