በአማራ ክልል ታስረው የነበሩ ዳኞች በሙሉ መለቀቃቸውን ማኅበሩ አስታወቀ

ፎቶ ፋይል፦ ባህር ዳር

በአማራ ክልል በተለያየ ጊዜ ታስረው የነበሩ 13 ዳኞች ከእስር መለቀቃቸውን የክልሉ የዳኞች ማኅበር አስታወቀ። ዳኞቹ የተለቀቁት በተለያየ ጊዜ መኾኑን የተናገሩት፣ የማኅበሩ ተወካይ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ አሳሳ ፣ካለፈው ሳምንት ጀምሮ እስከ ትላንት በስቲያ ድረስ የቀሩት አምስት ዳኞች መለቀቃቸውን ተናግረዋል።

እያንዳንዱ ዳኛ በምን ምክንያት እንደታሰረ እና እንደተለቀቀ ምንም የሚያውቁት ነገር እንደሌለ የተናገሩት አቶ ብርሃኑ እንደ ማኅበር ግን ባለፈው ጥቅምት ወር 13 ዳኞች በሥራቸው ምክንያት መታሰራቸውን መግለጫ አውጥተው እንደነበር አስታውሰዋል።

Your browser doesn’t support HTML5

በአማራ ክልል ታስረው የነበሩ ዳኞች በሙሉ መለቀቃቸውን ማኅበሩ አስታወቀ

በምስራቅ ጎጃም ዞን እነሴ ሳር ምድር ወረዳ ፍርድ ቤት ፕሬዝደት የነበሩትና ለአራት ወራት ያህል ታስረው ባለፈው ጥር 10 ቀን 2017 ዓ.ም የተለቀቁት አቶ ዘላለም ተመቸው በተጠረጠሩበት ወንጀን ታስረው ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ መለቀቃቸውን ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።