በድርቅ የተጎዱ አርሶ አደሮች ለምግብ እጥረት ተጋልጠናል አሉ

Your browser doesn’t support HTML5

በደቡብ ክልል ቡርጂ ልዩ ወረዳ በድርቅ የተጎዱ አርሶ አደሮች ለምግብ እጥረት መጋለጣቸውንና በቂ የሰብዓዊ እርዳታም እንደማያገኙ ተናገሩ። አርሶ አደሮቹ የክልሉና ፌዴራል መንግሥታት፣ እንዲሁም አጋር ድርጅቶች እንዲደግፏቸው ጠይቀዋል

በቡርጂ ልየ ወረዳ በተከሰተው ድርቅ ከ83 ሺህ በላይ ሰዎች አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው የወረዳው አስተዳደር አስታውቋል።

በድርቁ የተነሳ ከ11 ሺህ በላይ እንስሳት ሲሞቱ 5 መቶ ሺህ እንሰሳት አስቸኳይ የመኖ አቅርቦት ካላገኙ ተመሳሳይ ዕጣ እንደሚጠብቃቸውም ተመልክቷል።

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።