በመተማ የእርሻ ቦታ ኢትዮጵያውያን በሱዳን ታጣቂዎች መገደላቸውና መቁሰላቸን ነዋሪዎች ተናገሩ

መተማ ሆስፒታል

በመተማ "ደለሎ ቁጥር አራት”በተባለ የእርሻ ቦታ ላይ በእርሻ ሥራ ላይ የነበሩ ኢትዮጵያውያን በሱዳን ታጣቂዎች መገደላቸውን፣ ሁለት የመከላከያ ሰራዊት አባላትን ጨምሮ ደግሞ ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች መቁሰላቸውን ነዋሪዎችና የሆስፒታል ምንጮች ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።

በኢትዮጵያና በሱዳን ድንበር “ደለሎ ቁጥር አራት”- በተባለ የእርሻ ቦታ ላይ የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች ከሱዳን ታጣቂዎች ጋራ ውጊያ መግጠማቸው በአካባቢው የሚገኙ ነዋሪዎች ተናገሩ።

ከሆስፒታል ያገኘነው መረጃ ቁስለኞች ከቦታው እየመጡ መሆኑና በነበረው ውጊያ ሰዎች መሞታቸውን እየተናገሩ መሆኑን ገልፀውልናል።

(ዝርዝሩን ከተያይዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)

Your browser doesn’t support HTML5

በመተማ የእርሻ ቦታ ኢትዮጵያውያን በሱዳን ታጣቂዎች ሰዎች መገደላቸውና መቁሰላቸን ነዋሪዎች ተናገሩ