የታገዱት የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ህልውናቸው አደጋ ላይ መውደቁን መሪዎቹ ገለጹ

የመብቶች እና የዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል፤ ካርድ ኢትዮጵያ

ኢትዮጵያ ውስጥ በቅርቡ ከታገዱት ሦስት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የሁለቱ አመራሮች የድርጅታቸው ሕልውና አደጋ ላይ መውደቁን ተናገሩ።

የመብቶችና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (ካርድ) እና የሕግ ባለሞያዎች ለሰብአዊ መብቶች የተባሉ ሁለቱ የሲቪል ማኅበራት ድርጅት መሪዎች የባንክ ሂሳባቸው በመታገዱ ምክኒያት፣ ለሠራተኞች ደሞዝ መክፈልን ጨምሮ ምንም ዐይነት እንቅስቃሴ ማድረግ ባለመቻላቸው ችግር ውስጥ መውደቃቸውን ገለጹ።

Your browser doesn’t support HTML5

የታገዱት የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ህልውናቸው አደጋ ላይ መውደቁን መሪዎቹ ገለጹ

ከኢትዮጵያ በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረገው ጥረት አልተሳካም። ይኹንና ኅዳር 19 ቀን 2017 ዓ.ም. የተቋሙ ምክትል ዲሬክተር አቶ ፋሲካው ሞላ፣ እየተከናወነ ነው ያሏቸው የማጣራት ሥራ ሲጠናቀቅ ውጤቱ እንደሚገለጽ በቅርቡ መናገራቸው ይታወሳል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።