ቲክ ቶክን በአሜሪካ ለማገድ የወጣው ሕግ ቻይናን አስቆጥቷል

Your browser doesn’t support HTML5

ቲክ ቶክን በአሜሪካ ለማገድ የወጣው ሕግ ቻይናን አስቆጥቷል

ቲክ ቶክ፤ በቻይና መንግስት ቁጥጥር ሥር እንደሆነ ከሚነገረው እናት ኩባንያው ባይት ዳንስ ካልተላቀቀ፣ መተገበሪያው በአሜሪካ ጥቅም እንዳይውል የዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ም/ቤት ትናንት ረቡዕ አንድ ሕግ ማውጣቱን ተከትሉ፣ የቻይና መንግስት ቁጣውን አሰምቷል።

በሌላ በኩል ደግሞ ትናንት በተወካዮች ም/ቤት የፀደቀው ሕግ የንግግር ነፃነትን የሚገድብ ነው በሚል በሕግ አውጪው ሸንጎ ወይም ሴኔት ላይፀድቅ ይችላል ተብሏል።

ከቪኦኤዋ የኮንግረስ ዘጋቢ ካትሪን ጂፕሰን እንዲሁም ከአሶስዬትድ ፕረስ ያገኘነውን ዘገባዎች ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።