በጃን ሜዳ ብፁዕ አቡነ ናትናዔል፤ በሎስ አንጀለስ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ቡራኬ ሰጡ፡፡
“ድምፃችን ይሰማ” በሚል ርዕስ የኢትዮጵያ ሙስሊም ማኅበረሰብ አባላት ለመንግሥት ጥያቄ ያቀረቡበትን አንደኛ ዓመት በተለያዩ እንቅስቃሴዎች ሰሞኑን አስበዋል፡፡
በፈጣን ሁኔታ እያበበ ባለው የኤርትራ የማዕድን ዘርፍ ላይ መዋዕለ ነዋይ የሚያፈስሱ ዓለምአቀፍ ኩባንያዎች የጥንቃቄ እርምጃ ካልወሰዱ በሰብዓዊ መብቶች ረገጣ ውስጥ ተሣታፊ የመሆን አደጋ እንደሚጠብቃቸው ሂዩማን ራይትስ ዋች አስታውቋል፡፡ በማዕድን ልማት ሥራው ላይ የተሠማራው የውጭ ኩባንያ “የግዳጅ ሥራ አይፈቀድም” ብሏል፡፡
በጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ ላይ የበታች ፍርድ ቤት የሰጠውን ውሳኔ የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ማፅናቱ ያሣዘናቸው መሆኑን ዓለምአቀፉ የሴቶች የመገናኛ ብዙኃን ድርጅት - IWMF እና ዓለምአቀፉ የጋዜጠኞች ደኅንነት ተሟጋች ድርጅት - ሲፒጄ አስታውቀዋል፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ ሕግ አውጭዎች ባለፈው ዓመት ማብቂያ እና ትናንትን የከረሙበት ትንቅንቅ ሌሊቱን በከፊል መፍትሔ አግኝቶ አድሯል፡፡
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከሕግ መወሰኛው በሚቀርብለት የሕግ ረቂቅ ላይ ድምፅ ለመስጠት ዛሬ ከቀኑ ስምንት ሰዓት፣ በአዲስ አበባ አቆጣጠር ከምሽቱ አራት ሰዓት ላይ ይሰበሰባል፡፡
በአንድ ሰዓት ውስጥ የአሜሪካ ፖለቲከኛ ሰዎች “ፊስካል ክሊፍ” ብለው የጠሩትን በጀት አፋፍ ታልፋለች፡፡ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ ባይደን ኮንግረሱ ውስጥ ተገኝተው ከሴኔቱ የአብዝኀና የአናሣ መሪዎች ጋር ሙሉ ማምሻውን እየመከሩ ነው፡፡
በዋሽንግተን ዲሲና አባባቢዋ ያሉ የተወሰኑ ትውልደ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊያን ዕሁድ ታኅሣስ 21 / 2005 ምሽት ላይ ሻማ የማብራት ሥነ-ሥርዓት አካሂደዋል፡፡
ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ከኔክቲከት ክፍለሃገር ውስጥ ሰሞኑን በአንድ የአንደኛ ትምህርት ቤት ሕፃናትና በመምህራኑ ላይ በአንድ ግለሰብ የተፈፀመው ግድያ ብዙ ንግግሮችንና ውይይቶችን እያጫረ ነው፡፡
በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል፤ በቤንች ማጂ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ የሚኖሩ፤ ከዓመታት በፊት ከአማራ ክልል የሄዱ ሠፋሪ አርሦ አደሮች በአካባቢው ባለሥልጣናት ተገድደው ቀያቸውን ልንዲለቅቁ እየተደረጉ መሆኑን መዘገባችን ይታወሳል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአጋሮች ጉባዔ ለ18ኛ ጊዜ ዶሃ ላይ ተቀምጧል፡፡
የዘንድሮው የዓለም የኤድስ ቀን የታሰበውና ፀረ-ኤድስ እንቅስቃሴዎቹም የሚካሄዱት “ዜሮ ማግለል፣ ዜሮ በኤችአይቪ መያዝ፣ ዜሮ የኤድስ ሞት” በሚል መርኅ ነው፡፡
ጂማ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ትናንት ተፈጥሯል በተባለ ችግር ከፖሊስ ጋር ግጭት እንደነበረ አንዳንድ ተማሪዎች ሲገልፁ የተፈጠረ ግጭትም ይሁን የተጎዳ ተማሪ አለመኖሩን የተማሪዎቹ ኅብረት ፕሬዚዳንት እና የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዚዳንት ለቪኦኤ ገለፁ፡፡
“ይቻላል” ይላሉ በትግሉ መስክ በግንባር የተሠማሩት ተዋንያን፡፡ ያንን እጅግ ከባድ የሚመስል ግብ ለመድረስ የቆረጡም ይመስላሉ፡፡
የዘንድሮው የዓለም የኤድስ ቀን እየታሰበ ያለው “ዜሮ ማግለል፣ ዜሮ በኤችአይቪ መያዝ፣ ዜሮ የኤድስ ሞት” በሚል መርኅ ነው፡፡
የተባበሩት መንግሥታት የዓለም የሥራ ድርጅት - አይኤልኦ ኢትዮጵያን የሠራተኞችን መብቶች በማክበር በኩል የከፋች ሃገር ናት ሲል በቅርቡ ሪፖርት አውጥቷል፡፡
በኢትዮጵያ ለሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት መመረጥ ላይ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽነሯ እና የሰመጉ ዳይሬክተር ለቪኦኤ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በድጋሚ ከተመረጡ ወዲህም ሆነ ላለፉት ስምንት ወራት የመጀመሪያ የሆነ ሰፊ ጋዜጣዊ መግለጫ ትናንት በዋይት ኃውስ ለተገኙ ጋዜጠኞች ሰጥተዋል፡፡
በሰብዓዊ መብቶች አያያዛቸው ላይ ጥያቄ ያለባቸው ሃገሮች በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ የድርጅቱ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባል ተደርገዋል ሲሉ የመብቶች ተሟጋች ቡድኖች ቅሬታቸውን አሰምተዋል፡፡
የአነስተኛ ባለይዞታ ገበሬዎችን አቅም ለማሣደግና የገበያ አቅርቦታቸውን ለማሻሻል በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ የተነጋገረ ዓለም አቀፍ ስብሰባ ባለፈው ሣምንት አዲስ አበባ ላይ ተካሂዷል፡፡
ተጨማሪ ይጫኑ