ኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ላይ ሲካሄድ የሰነበተው በእግሊዝኛ ስሙ ምኅፃር (WTO) እየተባለ የሚታወቀው የዓለም የንግድ ድርጅት ጉባዔ ዛሬ ማምሻውን ተጠናቀቀ። ድርጅቱ በዘንድሮው ስብሰባ የላይቤርያንና የአፍጋንስታንን የአባልነት ጥያቄ አጽድቋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ተቃውሞ በሚያሰሙ ኦሮሞዎች ላይ የሃይል እርምጃ እየወሰደ ነው ሲሉ በኬንያ የስደተኞች ማሕበረሰብ አባላት ባለፈው ሳምንት ውስጥ ናይሮቢ ላይ የተቃውሞ ስብሰባ አካሄዱ።
ኢትዮጵያና ኬንያ በሁለቱ ሀገራት ድምበር ከተማ በሆነችዉ ሞያሌ ዉስጥ በኢኮኖሚና ጸጥታ ጉዳይ ላይ የሚያተኩር ስምምነት ተፈራረሙ። በዚህ የስምምነት ፊርማ ስነ-ሥርዓት ላይም የሁለቱ ሀገራት መሪዎችና ምንስትሮች ተገኝተዋል።