ለዚህ ምክንያቱ ምንድነው? ችግሩን እንዴት መፍታት ይቻላል? በሚለው ላይ ለመወያየት ስመኝሽ የቆየ በአሜሪካ የመድሃኒት ቁጥጥር አስተዳደር መስሪያ ቤት ውስጥ በፔዲያትሪክ ፋርማኮሎጂስትነት የምታገለግለውን ዶክተር ሊሊ ሙሉጌታ እና የማህበረሰብ ጥናት ባለሙያ እና በአፍሪካ ዲያስፖራ ማህበረሰብ ኮሌጅ ተደራሽነት ዙሪያ የሚሰራ ተቋም መስራች ማቲዮስ መስፍንን ስቱዲዮ ጋብዛ አነጋግራለች።
ራሳቸውን የሚያጠፉ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ወጣቶች ቁጥር ለምን ጨመረ?
አሜሪካ ውስጥ በየ11 ደቂቃው አንድ ሰው ራሱን እንደሚያጠፋ የበሽታ መከላከያ እና መቆጣጠሪያ መስሪያቤት መረጃ ያሳያል። ባለፈው ዓመት ብቻ ወደ 50 ሺህ የሚጠጉ አሜሪካውያን ራሳቸውን አጥፍተዋል። በተለይ እድሜያቸው ከ10 - 24 ዓመት ባሉ ወጣቶች ዘንድ ዋና የሞት መንስዔ መሆኑንም ተመልክቷል። ይህ ቁጥር ትውልደ ኢትዮጵያዊ ወጣቶችንም ያጠቃልላል። ቁጥሩ በጥናት ባይረጋገጥም፣ ራሳቸውን የሚያጠፉ ኢትዮጵያዊ አሜሪካውያን ወጣቶች ቁጥር እየጨምረ መሄዱን ባለሙያዎች ይናገራሉ።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ማርች 14, 2025
በአፍሪካ የኅይል አቅርቦት ላይ ያተኮረውና በዋሽንግተን ዲሲ የተካሔደው ጉባኤ
-
ማርች 14, 2025
የኢትዮጵያውያት ሴቶች ጥያቄ ምንድን ነው? - የአድማጭ ተመልካቾች አስተያየት
-
ማርች 13, 2025
አርቲስት አንዱዓለም ጎሣ ተጨማሪ 13 ቀናትን በእስር እንዲቆይ ፍርድ ቤት ፈቀደ
-
ማርች 13, 2025
ሩሲያ የተቆጣጠረቻቸውን የዩክሬን ግዛቶች እንደያዘች መቀጠል ትሻለች