በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ረሃብ በአፍሪካ

ድርቅ በተጎዱ የደቡብ ኢትዮጵያ አካባቢዎች የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት ጠቃሚ አማራጭ እንደኾነላቸው አምራቾች ተናገሩ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:30 0:00

ዝናም አጠር በኾኑና ድርቅ ከብቶቻቸውን በአሳጣቸው የደቡብ ኢትዮጵያ አካባቢዎች፣ ከአንድ ዓመት በፊት የተጀመረው፣ የ30-40-30 የፍራፍሬ ፕሮጀክት፣ ጥቅም እያስገኘላቸው እንደኾነ፣ ፕሮጀክቱ አስቀድሞ የተጀረበት የደቡብ ኦሞ ዞን አርሶ እና አርብቶ አደሮች ተናገሩ።

የ30-40-30 የፍራፍሬ ፕሮጀክት፣ በክልሉ የሚገኙ አርሶ እና አርብቶ አደሮችን ተጠቃሚ ለማድረግ ሲባል፣ ከአንድ ዓመት በፊት የተጀመረ ነው፡፡ በፕሮጀክቱ መሠረት፣ አንድ አርሶ ወይም አርብቶ አደር በማሳው ላይ፣ አንድ መቶ የፍራፍሬ ችግኞች ይኖሩታል፡፡

ትምህርት ቤቶች እና ሃይማኖታዊ ተቋማት እንዲሁም ዩኒቨርሲቲዎችም፣ እስከ 10ሺሕ የፍራፍሬ ዛፎች እንዲኖራቸው የሚያስችል ፕሮጀክት እንደኾነ፣ የሐሳቡ አመንጪ እና የክልሉ የግብርና ቢሮ ሓላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር፣ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።

ሙሉውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

በትግራይ ክልል የጦርነቱ ክትያ የኾነው የረኀብ አደጋ ተባብሶ ቀጥሏል
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:58 0:00

አንዲት እጅግ የከሳች ሕፃን፣ ጥቅልል ብላ ከተኛችበት የሆስፒታል አልጋ ላይ ሳለች ለመተንፈስ ስትታገል ትታያለች። ወላጅ አባቷ፥ የልጅነት ለስላሳ ፊቷን ሲደባብስ፣ እናቷ በበኩሏ በተቀመጠችበት ታለቅሳለች።

ከፊት ለፊት ‘ቆንጆ’ የሚል ጽሑፍ የሚነበብበት ሮዝ ቀለም ያለው ሹራብ የለበሰችው አዳጊ ጽጌ ሲሳይ፥ 10 ዓመት ቢሞላትም ክብደቷ የሚመዝነው ግን 10 ኪሎ ግራም ብቻ ነው።

መነሻውን በክልሉ አድርጎ ለሁለት ዓመታት በተካሔደው ጦርነት እና በተከተለው ድርቅ ክፉኛ በተጎዳው ክልል፣ ለተከሠተው ከፍተኛ የምግብ እጥረት፣ ዐዲስ ሰለባ የኾነችው ሕፃን ለኅልፈት መዳረጓን ሐኪሟ ይናገራል።

የሮይተርስ የዜና ወኪል ወደ ሥፍራው የላካቸው ዘጋቢዎች፣ መቐለን ጨምሮ ተፈናቃዮች ያሉባቸውን የተለያዩ ከተሞች እና አካባቢዎች ተዘዋውረው ከተመለከቱ በኋላ ያጠናቀሩት ዘገባ ዝርዝሩን ይዟል።

ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG