በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ረሃብ በአፍሪካ

ምሥራቅ ወለጋ ውስጥ ለረኀብ ከተጋለጡ ተፈናቃዮች ራሳቸውን ያጠፉ እንዳሉ ተገለጸ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:55 0:00

በኦሮሚያ ክልል ከምሥራቅ ወለጋ እና ሆሮ ጉድሩ ዞኖች አምስት ወረዳዎች ተፈናቅለው፣ በምዕራብ ወለጋ ዞን “ሀሮ” በተባለ ቦታ የተሰባሰቡ ተፈናቃዮች፣ ለረኀብ መጋለጣቸውን ተናገሩ፡፡

በተለያዩ ጊዜያት በአካባቢው በነበረ ግጭት፣ ቀዬአቸውን ለቀው በምዕራብ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ ልዩ ስሙ “ሀሮ” በተባለ ቦታ ላይ፣ ያለመጠለያ እንደሚገኙ የሚናገሩት ተፈናቃዮቹ፣ ሰብአዊ ድጋፍ እና የሕክምና አገልግሎት፣ ከመንግሥት አግኝተው እንደማያውቁ ተናግረዋል።

በተያያዘም፣ ባለፈው ሳምንት፣ ዓለማየሁ ገብረ ሐና እና ሑሴን ፈንቴ የተባሉ ተፈናቃዮች፣ ልጆቻቸው ሲራቡ ማየት እንደማይፈልጉ ገልጸው፣ ራሳቸውን መርዘው እንዳጠፉ፣ ቤተሰቦቻቸው እና ሌሎች ተፈናቃዮች፣ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡

በተያዘው ሰኔ ወር ብቻ፣ ራሳቸውን ካጠፉት ሰዎች በተጨማሪ፣ ሦስት እናቶች በወሊድ፣ ሁለት ሕፃናት ደግሞ በሕክምና ዕጦት ምክንያት እንደሞቱ፣ ተፈናቃዮቹ አስረድተዋል፡፡

በሐምሌ ወር 2013 ዓ.ም.፣ በአካባቢው በነበረው ግጭት ተፈናቅለው “ሀሮ” በተባለ ቦታ እንደሚገኙ የተናገሩት ተፈናቃዮቹ፣ በ2014 ታኅሣሥ ወር ላይ ብቻ፣ የርዳታ እህል እንደተሰጣቸው ተናግረዋል፡፡

የምሥራቅ ወለጋ ቡሳ ጎኖፋ ወረዳ ጽሕፈት ቤት ሓላፊ ዳኜ ለቺሳ፣ 55 ሺሕ የሚደርሱ ተፈናቃዮች በወረዳው ቢኖሩም፣ በቦረና በተከሠተው ድርቅ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የርዳታ አሰጣጥ፣ ሰሞኑን ወደ ዞኑ የርዳታ እህል በመግባቱ፣ መሠራጨት እንደሚጀምር አመልክተዋል፡፡

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ያዳምጡ።

በድርቅ እና የጸጥታ ችግር የተባባሰው የኮሌራ ወረርሽኝ በኦሮሚያ ክልል ደቡባዊ ዞኖች እየተዛመተ ነው
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:35 0:00

በድርቅ በተጠቁት እና የጸጥታ ችግር ባለባቸው በኦሮሚያ ክልል ደቡባዊ ዞኖች፣ የኮሌራ ወረርሽኝ አሁንም እየተዛመተ እንደኾነ፣ የክልሉ ጤና ቢሮ ገለጸ።

በኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ የሕዝብ ጤና አጠባበቅ ዘርፍ ሓላፊ አቶ ገመቹ ሹሚ፣ ወረርሽኙ፥ ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር፣ በባሌ ዞን ከተከሠተ ወዲህ፣ የ81 ሰዎችን ሕይወት መቅጠፉን ጠቅሰው፣ አሁን ደግሞ፣ በድርቅ በተጠቁ የክልሉ ዞኖች ውስጥ እየተዛመተ እንደሆነ ተናግረዋል።

በሽታው፣ በቦረና ዞን ከዱብሉቅ ከተማ በቅርብ ርቀት ወደሚገኘው የተፈናቃዮች መጠለያ መግባቱንም፣ የዱብሉቅ ወረዳ አስተዳደር ባልደረባ፣ ለአሜሪካ ድምፅ ገልጸዋል።

የኦሮሚያ ጤና ቢሮ በበኩሉ፣ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር፣ ድርቅ እና የጸጥታ ችግሮች ዕንቅፋት እንደሆኑበት ይናገራል፡፡ ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG