"በህወሓት የወጣው መግለጫ ለውጡ ከመጣለት ሳይሆን ከመጣበት፣ ህዝብን የማይወክል አካል የወጣ ነው" ሲሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅሕፈት ቤት የፕሬስ ኃላፊ ንጉሡ ጥላሁን በሰጡት ምላሽ ተናግረዋል። “ለዚህም ምክንያቱ መግለጫውን ያወጣው ቡድን በለውጡ ምክንያት የተቋረጠበት ጥቅም መኖሩና የነበረው ግፍ እንዲመለስ መመኘቱ ነው” ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አሕመድ ያሸነፉት የዘንድሮ የኖቤል የሰላም ሽልማት ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተበረከተ የአደራ ሽልማት ነው ሲል ጽህፈት ቤታቸው አስታወቀ።
በኢትዮጵያ ታላቁ ቤተመንግሥት የተገነባው አንድነት ፓርክ የኢትዮጵያና የምስራቅ አፍሪካ መሪዎች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ከጥቂት ቀናት በኋላም ለሕዝብ ክፍት እንደሚሆን ይጠበቃል።
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ምኒስትር ዐብይ አህመድ እስራኤል የሚገኙ ኤርትራውያን ጥገኝነት ጠያቂዎች ወደሃገራቸው መመለስን ጉዳይ አስመልክቶ ከቤንጃሚን ኔታንያሁ ጋር ያደረጉት ውይይት የለም ሲሉ የፅህፈት ቤታቸውን ምንጮች ለአሜሪካ ድምፅ ገለጡ።
በኦሮምያ ክልል የሚንቀሳቀሱ ዋና ዋና የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን ስምምነት መፈራረማቸውን ዘግበናል፡፡
ሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም በባህርዳርና በአዲስ አበባ የተፈፀሙትን ጥቃቶች የተመለከተው ምርመራ እንደቀጠለ መሆኑን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል እንደሻው ጣሰው ለአሜሪካ ድምፅ አስታውቀዋል፡፡ ምርመራው ዘግይቷል የሚባለው ነገርም ትክክል አይደለም ነው ያሉት ኮሚሽነሩ፡፡ የተወሰ ጊዜም እንደሚወስድ ይታወቅ እንደነበርም አብራርተዋል፡
ከከፋ ህዝብ የምንማረው ብዙ ነገር አለ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ አካባቢውን መጠበቁን እና ከተፈጥሮ ጋር ተስማምቶ ማኖሩን አድንቀዋል፡፡
“ኢትዮጵያን የማሳነስ ልምምድ ለልጆቻችን አናወርስም” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ተናገሩ። ኢትዮጵያ የበርካታ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እንደዚሁም የተለያዩ ሃይማኖቶች አገር መሆኗን ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግሥታቸው ሁሉም ተከባብረው የሚኖሩባት ታላቅ ሃገር ለመገንባት እንደሚሠራም አብራርተዋል።
ጋምቤላ ክልል ውስጥ ሁለት የረድዔት ሠራተኞች የተገደሉበትን ከአንድ ሣምንት በፊት የተፈፀመውን ጥቃት በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ አውግዟል።
የተሻለ እንጂ የከፋ ዘማን ተመልሶ እንዳይመጣ እውነተኛ ሽግግር ለልጆቻችን ማረጋገጥ ይኖርብናል ሲሉ ጠ/ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ተናገሩ፡፡
ዜጎቿ የሚፈልጓትን ሀገር ለመገንባት ቁልፉ ያለው እየተወሰዱ ባሉ የማሻሽያ ዕርምጃዎች ላይ መሆኑን ከመቼውም ጊዜ በላይ አምናለሁ ሲሉ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ማይክል ሬነር አስታወቁ፡፡
ሁሉም የሰብዓዊ ዕርዳታ ተቋማት በጋምቤላ ክልል የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ለጊዜው ማቋረጣቸውን በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት ሰብዓዊ ዕርዳታ አስተባባሪ አስታወቁ፡፡
ደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ሰሞኑን በተከሰተው መጤ-ጠል ጥቃት ብዙ ጉዳት እንደደረሰባቸው እየተናገሩ ናቸው። የኢትዮጵያ መንግሥት እየተፈፀሙ ያሉ ሁከቶችን በብርቱ ቃላት አውግዞ የደቡብ አፍሪካ ባለሥልጣናት አስፈላጊውን ጥበቃ እንዲያደርጉ አሳስቧል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በኮሪያ ጃፓንና እሥራኤል ያደረጉት ጉብኝት ለ2012 የተያዘውን ሦስት ሚሊዮን የሥራ ዕድል የመፍጠር ዕቅድ የሚያግዝ መሆኑን ቃል አቀባያቸው እስታወቁ።
"ህወሃትን የመሳሰሉ ፓርቲዎች ዳግም ወደ ሥልጣን ለመመለስ እንደ ኦነግ ካሉ ድርጅቶች ጋር አዲስ የፖለቲካ ግንባር እየፈጠሩና መሰል ድርጅቶችን እያሰባሰቡ ነው" ሲሉ የኢዴፓ ብሄራዊ ምክር ቤት አባልና የፓርቲው የቀድሞ ሊቀመንበር አቶ ልደቱ አያሌው ተናግረዋል።
ቀጣዩ ሃገር አቀፍ ምርጫ አመቺ ሁኔታ ለመፍጠር ለሚያስችል ጊዜ መራዘም እንዳለበት በአቶ አዳነ ታፈሰ የሚመራው የኢትዮጵያዊያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ - ኢዴፓ አሳሰበ።
“እኛ የሠራነውና የመጣው ውጤት የተራራቀ ነው” ያሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች ዛሬም የቅሬታ ቅጽ ሲሞሉ ውለዋል። የኦሮሚያና የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮዎች ደግሞ በአንዳንድ የአገሪቱ ትምሕርት ቤቶች በፈተና ሂደቱ ላይ የነበረው ችግር ሳይስተካከል ውጤቱ ይፋ መደረጉ ተገቢ አለመሆኑን ገልፀዋል።
የፊታችን 2012 ዓ.ም መገባደጃ ላይ እንደሚካሄድ የሚጠበቀው የኢትዮጵያ አጠቃላይ ምርጫ በሕገመንግሥቱ በተቀረፀው ማዕቀፍና ጊዜ እንዲካሄድ የገዥው ኢሕአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አቋም መያዙ ተገልጿል።
በዩናይትድ ስቴትስ የሚገኙ ለትርፍ ያልተቋቋሙ ድርጅቶች ሀገር ቤት ካሉ በጎ ፈቃደኛ ድርጅቶችና ግለሰቦች ጋር የተባበሩበት የሴት ተማሪዎች የኮምፒውተር ኮዲንግ ወይንም ቅመራ ሥልጠና ተጠናቋል፡፡
ሃዲያ ዞን በደቡብ ክልል ችግር ከተፈጠረባቸው አካባቢዎች ጋር ተዳምሮ መጠቀሱና አስተዳዳሪውም መታገዳቸው ተጨባጩን ሁኔታ ያላገናዘበ እርምጃ ነው ሲሉ የዞኑ የሃገር ሽማግሌዎች ቅሬታ አሰምተዋል።
ተጨማሪ ይጫኑ