ትላንት በኬንያ ናይሮቢ ድርጀቱ ባደረገዉ ስብሰባ ከደርግ መንግስት ዉድቀት በኋላ በኢትዮጵያ ያለዉ የሰብዓዊ መብት ረገጣ እስካሁን ቀጥሎ ለብዙ የኢትዮጵያ ዜጎች መታሰርና መሰደድ ምክንያት ሆኗል ብሏል።
በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የተፈጥሮ አካባቢ ጥበቃ ጉባዔ በዓለማችን የአየር ንብረት ለውጥና ደኅንነት ጉዳዮች ላይ የሚተች ሁለተኛ ጉባዔ በናይሮቢ ላይ ተካሄደ።
ታንዛኒያ 74 የኢትዮጵያ ፍልሰተኞች ወደ ሃገራቸዉ የሚመለሱበትን መንገድ እንዲያመቻች የዓለም አቀፉ ፍልሰት ድርጅት (IOM) ጠየቀ። ፍለሰተኞቹ በታንዛኒያ ዉስጥ በህገ-ወጥ መንገድ በመግባት ተይዘዉ የእሥር ጊዜያቸዉን ከጨረሱ በኋላ ከሶስት ሳምንት በፊት ወደ ኬንያ ድምበር ሊሻገሩ የነበሩ ናቸዉ። የኬንያ መንግስት በጊዜዉ ፍልሰተኞቹ መመለስ ያለባቸዉ ወደ ትዉልድ ሃገራቸዉ ኢትዮጵያ እንጂ ወደ ኬንያ አይደለም ሲል ኢትዮጵያዉያኑ ወደ ድምበሩ እንዳይገቡ ፍቃድ ከልክሏቸዋል።
የኬንያ መንግስት በዳዳብና ካኩማ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ የሚገኘውን መስሪያ ቤት መዝጋቱን በጣቢያው የሚኖሩ ስደተኞች ተናገሩ። ስደተኞቹ እንደሚሉት የጣቢያው አስተዳደር የሆነዉ የኬንያ የስደተኞች ጉዳይ ቢሮ ቅርንጫፍ ከባለፈዉ ሳምንት መጨረሻ አንስቶ ሙሉ በሙሉ አገልግሎት መስጠት አቁሟል። የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ድርጅት (UNHCR) ሰኞ እለት ባወጣው መግለጫ የኬንያ መንግስት ዉሳኔዉን እንዲያጤን ጠይቋል። የኬንያ መንግስት እስካሁን በጉዳዩ ላይ የሰጠው መግለጫ የለም።
የኬንያ መንግሥት በሃገሪቱ ውስጥ የሚገኙ የስደተኞች መጠለያ ሠፈሮችን ለመዝጋት መወሰኑን አስታወቀ።
ፖሊስና የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች እስካሁን የደረሱበት ያልታወቀውን ሰዎች ለመታደግ ፍርስራሹን በማሰስ ላይ ናቸው። በአደጋው ከባድ ጉዳት የደረባቸው 12 ሰዎች በኬንያታ ሆስፒታል ሕክምና እያገኙ ናቸው። የአደጋው መንስዔ ናይሮቢ ላይ የጣለው ከባድ ዝናብ ሲሆን በተለይ ደግሞ ለሕንፃው መፍረስ ምክንያት እንደሆነ የተነገረው አጠገቡ ያለ ወንዝ መሙላቱ ነው።
የኢሉባቦር አሌ ወረዳ ነዋሪዎች፥ በወረዳቸዉ ከሚገኘዉ ከጉመሮ ሻይ ፋብሪካ፥ በቂ ጥቅም እያገኘን አይደለም ሲሉ ቅሬታቸዉን ለአሜርካ ድምጽ አሰሙ። ነዋሪዎቹ በተለይፋብሪካዉ የሰዉ ኃይል ሲቀጥር በቂ ዕድል ለአካባቢዉ ነዋሪዎች አይሰጥም ብለዉ አቤቱታ ሲያሰሙ፥ ፋብሪካዉ ግን የነዋሪዎቹን ጥቅም ለማስጠበቅ እየሰራሁ ነኝ ሲል መልስሰጥቷል።
በተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) የኦሮሞ አርብቶ አደሮች ማኅበርን ለአካባቢ ጥበቃና ለኢኮኖሚ ዕድገት አስተዋጽኦ አበርክታችኋል በማለት በስሙ (EQUATOR AWARD) የተሰኘዉን ሽልማት በናይሮቢ ሸለማቸዉ። UNDPን ወክለዉ ሽልማቱን ለማህበሩ መሪ ያበረከቱት ማይክል ባሊማ ማኅበሩ ቀጣይነት ላለዉ ዕድገትና ለአካባቢ ጥበቃ ያበረከተዉን አስተዋጽኦ አድንቀዋል።
ባለፈዉ እሁድ በሞያሌ ከተማ የጣለ ከባድ ዝናብ በሰዉ ሕይወትና በንብረት ላይ ጉዳት አደረሰ። ዝናቡን ተከትሎ በአካባቢዉ በደረሰ ከባድ ጎርፍ ማጥለቅለቅ የሶስት ሰዎች ሕይወት መጥፋቱን የአካባቢዉ የቀይ መስቀል ባልደረባ ለአሜርካ ድምጽ ተናግረዋል።
የአሜርካ ድምጽ ታሠሩ የተባሉትን ወጣቶች ጉዳይ አስመልክቶ፥ የአካባቢዉን የኦሮሚያ ክልል አስተዳደር ቢጠይቅም፥ ሃላፊዎቹ አስተያየት ለመስጠት ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል።
ፍለሰተኞቹ በህገ - ወጥ መንገድ ወደ ኬንያ በመግባት ቢከሰሱም የኪያምቡ ፍርድ ቤት ዳኛ የፍልሰተኞቹን ሁኔታ ከግንዛቤ በማስገባት የተለመደዉ ቅጣት ሳይጣልባቸዉ ወደ ሃገራቸዉ ይመለሱ በማለት ወሳኔ አስተላልፈዋል።
በህገ - ወጥ መንገድ ናይሮቢ ገቡ የተባሉ 23 ኢትዮጵያዉያን በኬንያ ፖሊስ በቁጥጥር ሥር ውለዋል። ኢትዮጵያውያኑ የተያዙት ሰሜን ናይሮቢ ካሃዋ ዌስት በሚባል ቦታ ነው። ትላንት ፍርድ ቤት መቅረባቸው ተገልጿል። ጉዳያቸዉን የተመለከተዉ የክያምቡ ግዛት ፍርድ ቤት በቂ ማስረጃና ምርመራ እስኪደረግ፥ የሳምንት ቀጠሮ ሰጥተዋቸዋል።
የኬንያ ፕሬዚደንት ኡሁሩ ኬንያታ ኬንያዉያንን ከጽንፈኞች ጥቃት ለመከላከል ተጨመሪ የፓሊስ ሃይል ያስፈልጋል አሉ።
ነዋሪዎቹ ይህ ችግር ከተቀሰቀሰበት ጊዜ አንስቶ አንድ አዛዉንት እና አንድ ህጻን ሕይወታቸዉ ሲያልፍ አንዲት ዕርጉዝ ሴት የጸነሰችዉ ጽንሥ በዚሁ በያዛት በሽታ መጨንገፉን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያዉያኑ ጉዳይ ፍርድ ቤት የቀረበዉ ባለፈዉ ዓርብ ሲሆን የኢሪንጋ ፍርድ ዉሳኔም ያልጠበቁት መሆኑን በእምቤያ ግዛት የኢንተርኔት ጋዜጠኛ ወይም ጦማሪ የሆነዉ ፍራይደይ ሲምባያ ለቪኦኤ ገልጿል።
የኢትዮጵያ ፍልሰተኞች ጉዳይ በታንዛንያ እስር ቤት።
በሕገ ወጥ መንገድ የኬንያን ድምበር ተሻግራችሁዋል በመባል የተከሰሱ ከ28 በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያዉያን ኦሮሞ ስደተኞች ወደ አገራቸዉ እንዲመለሱ የማርሳቢት ፍርድ ቤት መወሰኑ ታዉቋል። ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (UNHCR) ስደተኞቹ ጥገኝነት እንዲያገኙ ለኬንያ መንግስት ያቀረበዉ ጥያቄ አንድ ስደተኛ ከማስጠልል በስተቀር ተቀባይነት እንዳላገኘ ተናግሯል። እንዲመሰሱ የተደረጉት ስደተኞች ግን አሁን ያሉበት ሁኔታ አልታወቀም።
ኢዮጵያውያኑ በፖሊስ ቁጥጥር ስር በነበሩበት ጊዜ፣ ከረሃብና ከውኃ ጥም የተነሳ ሰዉነታቸዉ በጣም ተዳክሞ እንደነበረ የሃገሪቱ ፖሊስ አስታዉቀዋል። ባለሥልጣናት ለአሜርካ ድምጽ እንደተናገሩት፣ ሌሎች ህገ-ወጥ የተባሉ ኢትዮጵያውያንም በኬይላ ታንዛንያ እስር ቤት ዉስጥ ይገኛሉ።
ሰሜን ኬንያ ውስጥ ተይዘው በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ያሉት ጥገኝነት ፈላጊ የኢትዮጵያ ዜጎች መብታቸው እንዲከበር ኬንያ የሚገኘው የመንግሥታቱ ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር ቅርንጫፍ ጠየቀ።
ባለፈዉ ሳምንት ፍጻሜ ኬንያ ቁጥራቸዉ 25 የሚደርሱ ኢትዮጵያዉያን ጥገኝነት ጠያቂዎችን ለኢትዮጵያ መንግስት አሳልፋ ሰጠች ሲሉ በናይሮቢ የኦሮሞ ማህበረሰብ ተወካይ ተናገሩ።
ተጨማሪ ይጫኑ