በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ረሃብ በአፍሪካ

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቃል አቀባይ ስቴፋኒ ዱጃሪች
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቃል አቀባይ ስቴፋኒ ዱጃሪች

“የኢትዮጵያን የተለያዩ ክፍሎች፣ ኬንያን እና ሶማሊያን ይዞ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ ቀንድ ቁጥሩ 22 ሚሊዮን የሚገመት ሕዝብ ለከፋ የምግብ ዋስትና ዕጦት ተጋልጧል።” ሲሉ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቃል አቀባይ ስቴፋኒ ዱጃሪች በዛሬው መግለጫቸው ተናገሩ።

ቃል አቀባዩ አያይዘውም “በዓለም ምግብ ፕሮግራም ያሉ ባልደረቦቻችን እንደገለፁት በድርቅ በተጎዱት የሦስቱ ሀገራት የተለያዩ አካባቢዎች በዚህ ዓመት 5 ነጥብ 1 ሚሊዮን ህጻናት እጅግ ለበረታ የምግብ እጥረት እና የሰውነት መሟሸሽ ተጋልጠዋል።” ብለዋል።

‘የፊታችን መጋቢት ወር ይጥላል’ ተብሎ የሚጠበቀው ዝናብም ከአማካይ በታች እንደሚሆን ትንበያዎች አመላክተዋል። ዝናም ካልዘነበ እና ሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦቱ በሚፈለገው መጠን ካልደረሰ የምግብ ዋስትና ዕጦቱ እየተባባሰ እንደሚሄድም ያለሙ የምግብ ፕሮግራም አስጠንቅቋል።

በድርቁ ሳቢያ የተከሰተውን አስከፊ ረሃብ እና የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ለመቅረፍ ደብሊው ኤፍፒ የተቀናጀ የሁለትዮሽ አካሄድን በመከተል ላይ ነው ያሉት ዱጃሪች፣ “ከፍተኛ የአየር ንብረት መለዋወጥ የሚያስከትለውን ጉዳት የመቋቋም አቅምን በማጎልበት የህይወት

አድን አልሚ ምግቦች አቅርቦት በአፋጣኝ ማዳረስ መሆናቸውን አስረድተዋል።

ፎቶ ፋይል፦ በድርቅ ምክንያት ተፈናቅለው የተሰደዱ እርዳታ ለማግኘት እየተጠባበቁ፤ ባይዶዋ ሶማሊያ 10/12/2022
ፎቶ ፋይል፦ በድርቅ ምክንያት ተፈናቅለው የተሰደዱ እርዳታ ለማግኘት እየተጠባበቁ፤ ባይዶዋ ሶማሊያ 10/12/2022

በአፍሪካ ቀንድ ሀገሮች የሚከሰቱ ወረርሽኞች እና ከአየር ንብረት ጋር ተያያዥ የሆኑ አጣዳፊ አደጋዎች ቁጥር በዚህ ምዕት ዓመት ከምንጊዜውም በላይ እየጨመሩ መሆናቸው ተዘገበ። ይህም አስቀድሞም 47 ሚሊዮን ሰው ቸነፈር አፋፍ ላይ ባለበት ቀጣና ውስጥ ያለውን የጤና ቀውስ እያባባሰ መሆኑ ተገልጿል።

የሚበዛው የአፍሪካ ቀንድ አካባቢ በብርታቱ በአርባ ዓመታት ውስጥ ባልታየ ድርቅ እየተጠቃ ሲሆን አሁንም ለአምስተኛ ጊዜ መደበኛው ዝናብ አይጥልም የሚል ስጋት እንዳንዣበበ መሆኑ ይሰማል።

በሌላ በኩል ደግሞ በጎርፍ እና በግጭቶች የተጎዱ አካባቢዎችም እንዳሉ ይታወቃል።

የለየለት ቸነፈር ይከሰትባቸዋል የሚል ማስጠንቀቂያ ላይ ካሉት የሶማሊያ አካባቢዎች አንዷባይዶዋ መሆኗን የወደብ ከተማዪቱ የድርቅ ምላሽ አስተባባሪ ጄምስ ኢንዲቲያ አመልክተዋል።

በስፋት በቀጠለው ግጭት ምክንያት ብዙ ሰው ከመኖሪያው መፈናቀሉን የጠቆሙት ኢንዲቲያ ድርቅ በተከሰተ ቁጥር ድኅነቱ እየበረታ እንደሚሄድ ተናግረዋል።

ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG