በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ረሃብ በአፍሪካ

የዴንማርክ የአየር ንብረት ሚንስትር ዳን ጆርገንሰን
የዴንማርክ የአየር ንብረት ሚንስትር ዳን ጆርገንሰን

የዴንማርክ የአየር ንብረት ሚንስትር ዳን ጆርገንሰን ትናንት ረቡዕ የኢትዮጵያ የአፋር ክልልን ጎብኝተዋል፡፡ ድርቅ በተጠቃው የአፋር ክልል የሰሜን ኢትዮጵያን ጦርነት ለማቆም ባለፈው ህዳር የተደረሰውን ሥምምነት ተከትሎ የረድዔት እንቅስቃሴ መቀጠሉን ሮይተርስ የዓለም የምግብ ፕሮግራምን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡

በሰሜን ኢትዮጵያ ሲካሄድ የቆየው ጦርነት ብዙ መቶ ሺዎች ለረሃብ ሲዳርግ ብዙ ሺዎች መገደላቸውን እና አያሌ ሚሊዮን ሰዎች መፈናቀላቸውን ሮይተር አክሏል፡፡

በየቀኑ ለራሳቸው እና ለስድስት ልጆቻቸው ምግብ ሊቀበሉ ከመጠለያቸው ወደ የዓለም የምግብ ፕሮግራምን የምግብ ዕደላ ጣቢያ የሚመላለሱት ኡሮ ኮኖጆ ሙሉ በሙሉ የሚተማመኑት በሚሰጣቸው ዕርዳታ ላይ ብቻ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የዴንማርክ የአየር ንብረት ሚንስትር ዳን ጆርገንሰን “በተለይ የበለጸጉት ሀገሮች ትልቅ ኃላፊነት አለባቸው፡፡ አንዱ ኃላፊነታችን የካርቦን ልቀታችንን መቀነስ ነው፡፡ ይህን ሳናደርግ ስንቀር የሚሆነውን እያየን ነው የአየር ንብረት ለውጥ ህዝብን ይጎዳል፡፡ ደግሞም ጉዳቱ ወደፊት የሚመጣ ሳይሆን አሁን እየደረሰ ነው” ብለዋል፡፡

“የችግሩ መንስዔ መሆናቸው ሲነገር የቆየው የበለጸጉት ሀገሮች የበለጠ ሥራ ይጠበቅባቸዋል” ሲሉም ሚንስትሩ አሳስበዋል፡፡

“ድርቁ አብዝቶ ጎድቶናል” ያሉት ኡሮ ኮኖጆ “ላለፉት ሦስት ዓመታት ዝናብ አላየንም፤ ከብቶቻችንም ሳር አላገኙም ብዙ ከብቶች ሞተውብኛል” ብለዋል፡፡ ምንም ዓይነት የገቢ ምንጭ እንደሌላቸው ገልጸዋል፡፡

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቃል አቀባይ ስቴፋኒ ዱጃሪች
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቃል አቀባይ ስቴፋኒ ዱጃሪች

“የኢትዮጵያን የተለያዩ ክፍሎች፣ ኬንያን እና ሶማሊያን ይዞ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ ቀንድ ቁጥሩ 22 ሚሊዮን የሚገመት ሕዝብ ለከፋ የምግብ ዋስትና ዕጦት ተጋልጧል።” ሲሉ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቃል አቀባይ ስቴፋኒ ዱጃሪች በዛሬው መግለጫቸው ተናገሩ።

ቃል አቀባዩ አያይዘውም “በዓለም ምግብ ፕሮግራም ያሉ ባልደረቦቻችን እንደገለፁት በድርቅ በተጎዱት የሦስቱ ሀገራት የተለያዩ አካባቢዎች በዚህ ዓመት 5 ነጥብ 1 ሚሊዮን ህጻናት እጅግ ለበረታ የምግብ እጥረት እና የሰውነት መሟሸሽ ተጋልጠዋል።” ብለዋል።

‘የፊታችን መጋቢት ወር ይጥላል’ ተብሎ የሚጠበቀው ዝናብም ከአማካይ በታች እንደሚሆን ትንበያዎች አመላክተዋል። ዝናም ካልዘነበ እና ሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦቱ በሚፈለገው መጠን ካልደረሰ የምግብ ዋስትና ዕጦቱ እየተባባሰ እንደሚሄድም ያለሙ የምግብ ፕሮግራም አስጠንቅቋል።

በድርቁ ሳቢያ የተከሰተውን አስከፊ ረሃብ እና የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ለመቅረፍ ደብሊው ኤፍፒ የተቀናጀ የሁለትዮሽ አካሄድን በመከተል ላይ ነው ያሉት ዱጃሪች፣ “ከፍተኛ የአየር ንብረት መለዋወጥ የሚያስከትለውን ጉዳት የመቋቋም አቅምን በማጎልበት የህይወት

አድን አልሚ ምግቦች አቅርቦት በአፋጣኝ ማዳረስ መሆናቸውን አስረድተዋል።

ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG