በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ረሃብ በአፍሪካ

የጎፋ ዞን የጎርፍ ተጠቂዎች ወደ ቀዬአቸው ለመመለስ ድጋፍ ጠየቁ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:56 0:00

በደቡብ ክልል ጎፋ ዞን ኡባ ደብረ ፀሐይ ወረዳ በደረሰው የጎርፍ አደጋ የተፈናቀሉ ሰዎች፣ ወደ ቀዬአቸው ለመመለስ ድጋፍ ጠየቁ። የጎፋ ዞን አስተዳደር የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር፣ የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም፣ ከ158 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ አስታውቋል።

የኡባ ደብረ ፀሐይ ወረዳ አስተዳዳሪ በበኩላቸው፣ የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም፣ ከክልሉ ቀይ መስቀል እና ከአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ጋራ በመተባበር፥ ቁሳቁሶች እየተሰባሰቡ፣ በጎርፍ የተጥለቀለቀው እየተጠረገ፣ የጎርፍ መውረጃው እየተጠለፈ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የአሜሪካ ድምፅ በስልክ ያነጋገራቸውና ጎርፍ ያፈናቀላቸው አቶ አብርሃም ዘኬዎስ፤ ቤታቸው በጎርፍ ተጠራርጎ በመወሰዱ መጠለያ አልባ መኾናቸውን ይናገራሉ። ቤታቸው ተሠርቶ ወደ ቀዬአቸው መመለሱን አብዝተው የሚፈልጉት ነገር እንደኾነ አመልክተዋል።

የስምንት ልጆች እናት መኾናቸውን የተናገሩት ሌላዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ዙፋን ታደሰም፣ ከአቶ አብርሃም ዘኬዎስ ጋራ ተመሳሳይ ጥያቄ አላቸው፡፡

የኡባ ደብረ ፀሐይ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ኢልቶ ኢፀና፣ የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም፣ ከክልሉ ቀይ መስቀል እና ከአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ጋራ በመተባበር ጥረት እየተደረገ መኾኑን ገልጸዋል።

ቤት ለመሥራት የሚረዱ ቁሳቁሶችን የመሰብሰብ፣ በጎርፍ የተጥለቀለቀውን የመጥረግ፣ የጎርፍ መውረጃውን የመጥለፍ ሥራ መጀመሩን፣ አቶ ኢልቶ ጨምረው ተናግረዋል።

የዞኑ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ጽሕፈት ቤት ሓላፊ አቶ ማርቆስ መሰለ፣ የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም፣ 158 ሚሊዮን 669ሺሕ 609 ብር እንደሚያስፈልግ ይናገራሉ።

አቶ ማርቆስ፣ 124 ሚሊዮን 226ሺሕ 244 የግለሰቦች ሀብት፤ ከ34 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ መሠረተ ልማቶች እና ማኅበራዊ ተቋማት መውደማቸውን አስታውቀዋል።

እንደ አቶ አብርሃም ያሉ ጎርፍ ያፈናቀላቸው ነዋሪዎች፥ ተጠልልው በሚገኙባቸው ትምህርት ቤቶች፣ ቤተ ክርስቲያንና ጤና ጣቢያ የሚደረግላቸውን ሰብአዊ ድጋፍ አድንቀው፤ በዚኽ መልኩ ግን መቀጠል ስለማይቻል፣ ለዘላቂ መፍትሔ ትኩረት እንዲሰጥ አበክረው ጠይቀዋል።

በአደጋው ለተጎዱት ነዋሪዎች፥ ከጋሞ፣ ከኮንሶ፣ ከደቡብ ኦሞ፣ ከማሌ ወረዳ እና ሌሎች አጎራባች ዞኖች እና ከክልል ቢሮዎች፣ እንዲሁም ከደቡብ ክልል ቀይ መስቀል ማኅበር፣ ሰብአዊ ድጋፍ እየቀረበላቸው እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በኡባ ደብረ ፀሐይ ወረዳ የጎርፍ አደጋ፥ 21 ሰዎች ሲሞቱ፣ 17 ሰዎች ከባድ፣ 89 ሰዎች ደግሞ ቀላል የአካል ጉዳት እንደረሰባቸው ያስታወሱት አቶ ማርቆስ፣ ወረዳው በውል በአደረገው ማጣራት፣ የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ከ5ሺሕ ወደ 2ሺሕ167 መቀነሱን አስታውቀዋል። በዚኹ ማጣራት፣ 217 ቤቶች በጎርፉ የተወሰዱ ሲኾን፣ ከ3ሺሕ500 በላይ የቤት እንስሳት መሞታቸው ተረጋግጧል።

በናይጄሪያ የከፋ የአልሚ ምግብ እጥረት ሕፃናትን እየጎዳ ነው
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:54 0:00

በዓለም አቀፍ ርዳታ ውስንነት ምክንያት፣ በሰሜን ምሥራቅ ናይጄሪያ፣ አራት ሚሊዮን ሰዎች ከፍተኛ የምግብ እጥረት እንደሚገጥማቸው፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታውቋል።

የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ(OCHA)፣ ጋዜጠኞችን ወደ አካባቢው በመውሰድ፣ የችግሩ አስከፊነት ያለበትን ደረጃ እንዲታዘቡ አድርጓል። የኑሮ ሩጫ በሚበዛበት የከተማው ማዕከል እና መንግሥት ከእስላማዊ ነውጠኞች ጋራ ጦርነት ላይ በሚገኝበት ኹኔታ፣ በከተማው የሚገኙ ሕፃናት፣ በግጭቱ ምክንያት የተባባሰው የምግብ እጥረት ተጎጂዎች ኾነዋል።

ቢንቱ ሓሳን የተባለችው እናት፣ የሁለት ዓመት ልጇን ይዛ ሆስፒታል ተገኝታለች። ልጁ ተዳክሞና በደሙ ውስጥ የሚገኘው የስኳር መጠን እጅግ ቀንሶ ይታያል። ቢንቱ ብዙ አጥታለች። “አራት ልጆች ወልጄ ነበር። ሁለቱ ልጆቼ በአልሚ ምግብ እጥረት ምክንያት ሞተዋል። ሁለት ቀርተውኛል። ከእነርሱም አንዱ ታሟል። ወደ እዚኽ እንድመጣ ተነግሮኝ ነው የመጣኹት፤” ስትል፣ እያለፈችበት ያለውን የመከራ ንብርብር ታስረዳለች፡፡

አራት ልጆች ወልጄ ነበር። ሁለቱ ልጆቼ በአልሚ ምግብ እጥረት ምክንያት ሞተዋል። ሁለት ቀርተውኛል። ከእነርሱም አንዱ ታሟል። ወደ እዚኽ እንድመጣ ተነግሮኝ ነው የመጣኹት፤”

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እንደሚለው፥ ቦርኖ፣ አዳማዋ እና ዮቤ በተባሉ ግዛቶች፣ 700 ሺሕ የሚኾኑ ልጆች ከፍተኛ የተመጣጣኝ ምግብ እጥረት ገጥሟቸዋል።

በሰኔ እና በመስከረም ባሉት ወራት ውስጥ፣ ኹኔታው የከፋ እንደሚኾን ተ.መ.ድ አስጠንቅቋል። ይህ ወቅት ወትሮዎንም፣ ቀደም ብሎ የተመረተው ምግብ ክምችት የሚያልቅበት ነው። ባለፈው ዓመት የበልግ ወቅት በተከሠተው ከባድ ጎርፍ ምክንያት ደግሞ ምርቱ ተስተጓጉሏል።

ማቲያስ ሽሜል የተመድ አስተባባሪ ናቸው። “600 ሺሕ ሄክታር የእርሻ መሬት በመውደሙ እና ታጥቦ በመወሰዱ፣ በቅርብ ጊዜያት ውስጥ ከባድ የምግብ እጥረት ያጋጥማል፤” ሲሉ አመልክተዋል፡፡

ለሁሉም የሚዳረስ በቂ የምግብ ርዳታም የለም። ራን በተባለውና ከካሜሩን ጋራ በሚዋሰነው ሥፍራ፣ ለስምንት ወራት ርዳታ አለማግኘታቸውን ነዋሪዎቹ ይናገራሉ።

600 ሺሕ ሄክታር የእርሻ መሬት በመውደሙ እና ታጥቦ በመወሰዱ፣ በቅርብ ጊዜያት ውስጥ ከባድ የምግብ እጥረት ያጋጥማል፤”

ኬሉ ሞዱ የተባለች ወላጅ፣ ያለበቂ ምግብ ልጆቿን ማጥባት እንደማትችል ትናገራለች። በመኾኑም ልጇ፣ በተመጣጣኝ ምግብ እጥረት ተጎድታለች። “ይህችን ልጅ በምወልድበት ወቅት በቂ የኾነ የጡት ወተት አልነበረኝም። ሕፃኗ ሽቅብ ይላትና ያስቀምጣት ጀመር፤” ትላለች፡፡

የምግብ እጥረቱ በከፊል የመጣው፣ ሩሲያ በዩክሬን ላይ በከፈተችው ጦርነት እና በሱዳን እየተካሔደ ባለው ግጭት ሳቢያ ነው።

ባለሥልጣናት እንደሚሉት ደግሞ፣ በናይጄሪያ የተከሠተው የዋጋ ግሽበት እና የገንዘብ ፖሊሲው፣ የሰዎችን ምግብ የመግዛት ዐቅም አዳክሟል።

ካራንቪር ሲንግ፣ በዩኒሴፍ የተመጣጣኝ ምግብ ሓላፊ ናቸው። እርሳቸው እንደሚሉት፣ ርዳታ ችግር ወዳለባቸው ሌሎች የዓለም ክፍሎች እየተላከ ቢኾንም፣ ናይጄሪያ አሁንም የምግብ አቅርቦት በማግኘት ላይ ናት። ሓላፊው አክለውም፣ “በዓለም ላይ ባሉ ሌሎች አጠቃላይ አጣዳፊ ጉዳዮች ምክንያት፣ ርዳታ ወደዚያው እየተላከ ነው። ኾኖም ለጊዜው በቂ አለን። በቀጣይ ግን ተጨማሪ ርዳታ እንሻለን፤”

የናይጄሪያ ጸጥታ ኃይሎች፣ የእስላማዊ ነውጠኞቹን የመዋጋት ዐቅም እጅግ አዳክመዋል። አገሪቱ ግን አሁንም በጦርነት ላይ ናት። ያ እስከሚያቆም ድረስ፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች፣ ሌላ ዐይነት ጦርነት አለባቸው - ረኀብ።

ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG