በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ረሃብ በአፍሪካ

የኢትዮጵያ መንግሥት ቃል አቀባይ አቶ ለገሰ ቱሉ
የኢትዮጵያ መንግሥት ቃል አቀባይ አቶ ለገሰ ቱሉ

ለኢትዮጵያ የሚላከው የምግብ ርዳታ፣ “ለተረጂዎች እየደረሰ አይደለም” በሚል፣ ሁለት ዋና ዓለም አቀፍ ለጋሾች፣ የእህል ርዳታ ለማቋረጥ የወሰዱትን ርምጃ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ተቃውሟል፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት ቃል አቀባይ አቶ ለገሰ ቱሉ፣ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፥ የዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ የልማት እና ተራድኦ ድርጅት/USAID/ እና የዓለም ምግብ ፕሮግራም/WFP/ የወሰኑት ውሳኔ፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን የሚቀጣ ነው፤ ብለዋል።

ባለፈው ሳምንት ኀሙስ፣ የአሜሪካ መንግሥት ዓለም አቀፍ የርዳታ ተቋም የኾነው ዩኤስኤይድ፣ ርዳታ በሚደርስበት መንገድ ዙሪያ፣ አመቺ እና አስተማማኝ የአሠራር ለውጥ እስኪደረግ ድረስ፣ የምግብ ርዳታ ሥርጭቱን ማቆሙን አስታውቆ ነበር። ከአንድ ቀን በኋላ ደግሞ፣ ተመሳሳይ ውሳኔውን ያሳወቀው የዓለም ፕሮግራም እንዲሁ፣ ለኢትዮጵያ ተጎጂዎች ሲያሠራጭ የቆየውን የምግብ ርዳታ፣ “ስርቆት በመንሰራፋቱ” ምክንያት ለጊዜው ማቆሙን አስታውቋል።

ውሳኔው፥ በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሔደው ጦርነት፣ በደቡብ እና ደቡብ ምሥራቅ በተከሠተው እና ሶማሊያንና የኬንያን የተወሰኑ ክፍሎችን በአጠቃው ድርቅ ምክንያት፣ ለከፍተኛ የምግብ እጥረት የተጋለጡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ይጎዳል።

ባለፈው ወር፣ ዩኤስኤይድ እና የዓለም ምግብ ፕሮግራም፣ ለትግራይ የሚላከው ርዳታ ለገበያ እንደሚቀርብ ከደረሱበት በኋላ፣ የምግብ ርዳታ እንዲቆም ማድረጋቸውን አስታውቀው ነበር። ኾኖም፣ ሁለቱም ተቋማት፣ የርዳታ እህሉን ከተረጂዎች ወስደው ለገበያ በማቅረብ ተጠያቂ የኾኑትን አካላት ለይተው አልገለጹም።

የመንግሥት ቃል አቀባይ አቶ ለገሰ ቱሉ በሰጡት መግለጫ፣ ርዳታውን የማቆሙ ውሳኔ “ፖለቲካዊ ነው” ያሉ ሲኾን፣ “መንግሥትን ብቻ ተጠያቂ ማድረግ ተቀባይነት የለውም፤” ብለዋል።

አክለውም፤ ”በጋራ ለማጣራት ስምምነት ከተደረሰ በኋላ መግለጫው ቀድሞ መሰጠቱ ትክክል አይደለም፤” ብለዋል።

መንግሥት፣ ባለፈው ዐርብ፣ ከዩኤስኤይድ ጋራ በመኾን በሰጠው መግለጫ፣ እጅግ አሳሳቢ የኾነውን የምግብ ርዳታ፣ ለተጎጂዎች እንዳይደርስ የማድረጉን ክፍተት ለመፍታት ቁርጠኝነቱን ገልጿል።

በድርቅ እና በተለያዩ ግጭቶች ምክንያት፣ በኢትዮጵያ፥ ከ20 ሚሊዮን በላይ የሚኾኑ ሰዎች፣ የምግብ ርዳታ ጠባቂዎች መኾናቸውን የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (UN-OCHA) ባለፈው ግንቦት ያወጣው መረጃ ያሳያል።

በተጨማሪም ኢትዮጵያ፣ ወደ አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ ስደተኞችን የምታስተናግድ ሲኾን፣ አብዛኞቹ፥ ከደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊያ እና ኤርትራ የመጡ ናቸው። ከሚያዝያ ወር አጋማሽ ጀምሮ ደግሞ፣ በሱዳን የተፈጠረውን ግጭት የሸሹ ወደ 30ሺሕ የሚጠጉ ሰዎች ኢትዮጵያ ውስጥ ተጠልለው ይገኛሉ።

የዓለም ምግብ ፕሮግራም የኢትዮጵያ የርዳታ ምግብ ሥርጭቱን ማቆሙን አስታወቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:07 0:00

የተባበሩት መንግሥታት የዓለም የምግብ ፕሮግራም(WFP)፣ ለኢትዮጵያ ተጎጂዎች ሲያሠራጭ የቆየውን የምግብ ርዳታ፣ “ስርቆት በመንሰራፋቱ” ምክንያት ለጊዜው ማቆሙን፣ ዛሬ አስታወቀ።

የዓለም ምግብ ፕሮግራም፣ የርዳታ ምግብ የማቆም ውሳኔውን ይፋ ያደረገው፣ ዩናይትድ ስቴትስ፣ ተመሳሳይ ርምጃ መውሰዷን፣ በዩኤስኤአይዲ በኩል ካሳወቀች ከአንድ ቀን በኋላ ነው።

የዓለም ምግብ ፕሮግራም ውሳኔን ተከትሎ፣ በሕዝብ ብዛት ከአፍሪካ ሁለተኛ በኾነችው ሀገር፣ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት የበለጠ ሊጨምር ይችላል፤ የሚል ስጋት አይሏል።

ውሳኔውን አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት፣ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዲሬክተር ሲንዲ ማኬይን፣ “የምግብ ርዳታ ለተረጂዎች እንዳይደርስ ማድረግ በፍጹም ተቀባይነት የለውም፤” ያሉ ሲኾን፣ የኢትዮጵያ መንግሥት፣ ሓላፊነት ያለባቸውን ለማጣራትና ተጠያቂ ለማድረግ ያሳየውን ቁርጠኝነት እንደሚያደንቁም ገልጸዋል።

በአፍሪካ ቀንድ፣ ባለፉት ዐሥርት ዓመታት ባልታየው ድርቅ እና በሰሜን ኢትዮጵያ ለሁለት ዓመታት በዘለቀውና በ10ሺሕ የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት ባጠፋው ግጭት ምክንያት፣ በኢትዮጵያ ከ20 ሚሊዮን በላይ የሚኾኑ ሰዎች፣ የምግብ ርዳታ ጠባቂዎች ናቸው፡፡ የዓለም ምግብ ፕሮግራም፣ በነዚኽ ሁለት ቀውሶች ምክንያት የተጎዱ፣ ሰባት ሚሊየን ሰዎችን ሲረዳ ቆይቷል።

የዓለም ምግብ ፕሮግራም(WFP) እና የዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ የልማት ተራድኦ ድርጅት(USAID)፣ ለውሳኔያቸው ምክንያት በኾነው፣ “የርዳታ ለተጎጂው አለመድረስ” ጉዳይ፣ ዝርዝር መረጃ ባይሰጡም፣ የዜና አውታሮች የተመለከቱትና ለለጋሽ አካላት የተሠራጨው መግለጫ፣ በፌደራል እና በክልል መንግሥታት ባለሥልጣናት የተቀናጀ የጥቅም ትስስር፣ የርዳታ ምግብ፣ ወደ ኢትዮጵያ ወታደራዊ ክፍሎች እንደሚዘዋወር አመልክቷል።

በዋናነት የሚያሳስበን፣ በእኛ ድጋፍ ላይ ጥገኛ የኾኑ በሚሊየን የሚቆጠሩ ረኀብተኞች ጉዳይ ነው፤ ያሉት የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዲሬክተር፣ በተቻለ ፍጥነት ሥራችንን ለመቀጠል፣ ከሁሉም አጋሮቻችን ጋራ ያለመታከት እንሠራለን፤ ብለዋል።

የዓለም ምግብ ፕሮግራም፥ ለሕፃናት፣ ለነፍሰ ጡሮች እና ለሚያጠቡ እናቶች የሚደረግ የተመጣጠነ ምግብ ርዳታ፣ የትምህርት ቤት ምገባ መርሐ ግብሮች፣ የአርሶ አደሮችንና አርብቶ አደሮችን ዐቅም ለመገንባት የሚደረጉ ድጋፎች ግን ሳይቋረጡ እንደሚቀጥሉ በመግለጫው አስታውቋል።

በሮይተርስ የተጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ያዳምጡ።

ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG