በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ረሃብ በአፍሪካ

በደቡብና ደቡብ ምስራቅ የኢትዮጵያ ክፍሎች የረሃብ ስጋት አለ
please wait

No media source currently available

0:00 0:08:08 0:00

በኢትዮጵያ ስድስት ተከታታይ ወቅት ዝናብ ላይጥል እንደሚችል በመገመቱ በደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ የኢትዮጵያ ክፍሎች ለረሃብ አደጋ ሊጋለጥ ይችላል ሲል አክሽን አጌንስት ሀንገር የተሰኘው በአፍሪካ ቀንድ ረሃብን ለማጥፋት የሚንቀሳቀሰው ዓለም አቀፍ ሰብዓዊ ርዳታ ሰጪ ተቋም አስጠነቀቀ።

በኢትዮጵያ እስካሁን ቢያንስ 12 ሚሊየን ሰዎች ለሞት ለሚዳርግ የድርቅ አደጋ መጋለጣቸውን እና ከ4.5 ሚሊየን በላይ የቀንድ ከብቶች መሞታቸውን የተቋሙ የኢትዮጵያ ፕሮግራም ዳይሬክተር ቤዛ አበበ ተናግረዋል።

ለከፋ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት የተጋለጡ ህፃናት ቁጥርም በከፍተኛ ሁኔታ እየጨምረ መሄዱን ዳይሬክተሯ ጨምረው ተናግረዋል።

በአዲስ አበባ እየተካሄደ ያለው የአፍሪካ ኅብረት ስብሰባ በቀጠናው እየከፋ የሄደውን ድርቅ ለመቅረፍ ቅድሚያ ሰጥቶ እንዲወያይም ጠይቀዋል።

ሙሉውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

በድርቅ ለተጠቃችው ሶማሊያ ትኩረት እንዲሰጥ ግሪንፊልድ ጠየቁ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:04 0:00

በድርቅ ምክኒያት ዜጎቿ ለረሃብ ለተጋለጡባት ሶማሊያ ለጋሾች ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተው ሰዎችን ከሞት እንዲታደጉ በተባበሩት መንግሥታት የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ሊንዳ ቶማስ ግሪንፊልድ ጠየቁ።

ሶማሊያን ጨምሮ በአራት የአፍሪካ ሀገሮች ጉብኝት ያደረጉት ግሪንፊልድ፤ ካሁኑ አስፈላጊው ድጋፍ ካልተደረገ በሶማሊያ የተከሰተው የምግብ እጥረት የብዙዎችን ህይወት ሊቀጥፍ እንደሚችል ስጋታቸውን ገልጸዋል፡፡

ዩናይትድ ስቴትስ በሶማሊያ ርሃብን ለመከላከል ተጨማሪ 40 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ እንደምትለግስ አምባሳደር ግሪንፊልድ ከጉብኝታቸው በኋላ በሰጡት መግለጫ ይፋ አድርገዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ዘገባ ያገኛሉ።

ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG