በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ረሃብ በአፍሪካ

ደቡብ ኦሮሚያ የድርቁ ጫና አሁንም እየከፋ ነዉ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:37 0:00

በኦሮሚያ ክልል ደቡባዊ ክፍል ድርቁ ያስከተለው ጫና የከፋ መሆኑን የጉጂ ዞን አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ልቤን ደበሶ በዞኑ በድርቅና በፀጥታ ችግር ምክኒያት ለችግር የተጋለጡ ከአምስት መቶ ሰባ ሺህ በላይ ነዋሪዎች የምግብ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ተናግረዋል። የተባበሩት መንግሥታት የእርዳታ ማስተባበርያ ቢሮም፣ በድርቅ የተጠቁ የኢትዮጵያ ክልሎች በኮሌራ ወረርሺኝም እየተጎዱ መሆኑን አስታውቋል።

በሌላ በኩል ለአምስት ተከታታይ ወቅቶች ዝናብ ባለመኖሩ ምክኒያት የተባባሳው የቦረና ድርቅ እስካሁን 3.3 ሚልየን እንስሳት መጨረሱን የዞኑ አስተዳደር ለአገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ይፋ አድርጓል።

ቦረና ውስጥ ድርቅ መበርታቱንና ነዋሪዎቹ በምግብ እጥረት እየተቸገሩ መሆናቸውን ጠቅሰን በተደጋጋሚ መዘገባችን ይታወሳል።

በተጨማሪም ወደ ስምንት መቶ ሺህ የሚሆን ሰው የምግብ ድጋፍ እንደሚያስፈልገውና ከእነዚህም ውስጥ አዛውንቶችና ሕፃናት በረሃብ እየተጎዱ መሆናቸውና የሚደርሰው የእርዳታ እህልም እጅግ አነስተኛ መሆኑን የቦረና ዞን ድሬ ወረዳ ነዋሪዎችና በአካባቢው የሚሰሩ የጤና ባለሞያ ከዚህ ቀደም ለአሜሪካ ድምፅ መናገራቸው አይዘነጋም።

የዘገባውን ሙሉ ይዘት ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

የአፍሪካ ቀንድ ከዚህ በፊት ከታየው የከፋ ቸነፈር ገጥሞታል
የአፍሪካ ቀንድ ከዚህ በፊት ከታየው የከፋ ቸነፈር ገጥሞታል

በአፍሪካ ቀንድ በአሁኑ ወቅት የሚታየው የድርቅ ሁኔታ ሩብ ሚሊዮን ሰዎችን ከገደለውና ከ 12 ዓመታት በፊት በእአአ 2011 ከታየው የባሰ እንደሆነ የቀጠናው የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) የአየር ትንበያ ማዕከል ዛሬ አስጥንቅቋል፡፡

ማዕከሉ በተጨማሪም በመጪው ሦስት ወራት ከተለመደው በታች የዝናብ መጠን እንደሚጠበቅ አስታውቋል፡፡ ይህም በሶማሊያ፣ በኢትዮጵያና ኬንያ ለስድስተኛ ተከታታይ ወቅት ዝናብ ሳይጥል እንደሚቀር አመላካች ነው ብሏል ማዕከሉ።

በሶማሊያ ለሦስት ዓመታት የቆየው ድርቅ በአሥር ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ሲገድል፣ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ደግሞ መፈናቀላቸውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያስታውቃል።

በሶማሊያ የተከሰተው ሞት ከ12 ዓመታት በፊት ከነበረው በእርግጠኝነት በሚባል ደረጃ እንደሚልቅ በአገሪቱ የተመድ አስተባባሪ አስጠንቅቀዋል።

በሶማሊያ፣ በኢትዮጵያና ኬንያ በድምሩ 23 ሚሊዮን ሰዎች ከፍተኛ የምግብ ዋስትና እጦት የተጋረጠባቸው መሆኑን የተመድ የምግብ ፕሮግራም (ፋኦ) አስታውቋል፡፡ 11 ሚሊዮን የሚሆኑ የቤት እንስሳት አልቀዋል፡፡

በዩክሬን እየተካሄደ ያለው ጦርነት በተለምዶ አፍሪካን ይረዱ የነበሩ የአውሮፓ ለጋሾች ትኩረታቸው እዛው እንዲቀር አድርጓል።

የኢጋድ ሊቀመንበር ወርቅነህ ገበየሁ መንግሥታትና አጋሮች በጣም ከመዘግየቱ በፊት መላ እንዲዘይዱ ጥሪ አድርገዋል።

ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG