በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ረሃብ በአፍሪካ

የአፍሪካ ቀንድ ከዚህ በፊት ከታየው የከፋ ቸነፈር ገጥሞታል
የአፍሪካ ቀንድ ከዚህ በፊት ከታየው የከፋ ቸነፈር ገጥሞታል

በአፍሪካ ቀንድ በአሁኑ ወቅት የሚታየው የድርቅ ሁኔታ ሩብ ሚሊዮን ሰዎችን ከገደለውና ከ 12 ዓመታት በፊት በእአአ 2011 ከታየው የባሰ እንደሆነ የቀጠናው የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) የአየር ትንበያ ማዕከል ዛሬ አስጥንቅቋል፡፡

ማዕከሉ በተጨማሪም በመጪው ሦስት ወራት ከተለመደው በታች የዝናብ መጠን እንደሚጠበቅ አስታውቋል፡፡ ይህም በሶማሊያ፣ በኢትዮጵያና ኬንያ ለስድስተኛ ተከታታይ ወቅት ዝናብ ሳይጥል እንደሚቀር አመላካች ነው ብሏል ማዕከሉ።

በሶማሊያ ለሦስት ዓመታት የቆየው ድርቅ በአሥር ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ሲገድል፣ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ደግሞ መፈናቀላቸውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያስታውቃል።

በሶማሊያ የተከሰተው ሞት ከ12 ዓመታት በፊት ከነበረው በእርግጠኝነት በሚባል ደረጃ እንደሚልቅ በአገሪቱ የተመድ አስተባባሪ አስጠንቅቀዋል።

በሶማሊያ፣ በኢትዮጵያና ኬንያ በድምሩ 23 ሚሊዮን ሰዎች ከፍተኛ የምግብ ዋስትና እጦት የተጋረጠባቸው መሆኑን የተመድ የምግብ ፕሮግራም (ፋኦ) አስታውቋል፡፡ 11 ሚሊዮን የሚሆኑ የቤት እንስሳት አልቀዋል፡፡

በዩክሬን እየተካሄደ ያለው ጦርነት በተለምዶ አፍሪካን ይረዱ የነበሩ የአውሮፓ ለጋሾች ትኩረታቸው እዛው እንዲቀር አድርጓል።

የኢጋድ ሊቀመንበር ወርቅነህ ገበየሁ መንግሥታትና አጋሮች በጣም ከመዘግየቱ በፊት መላ እንዲዘይዱ ጥሪ አድርገዋል።

ፎቶ ፋይል፦ የተፈናቀያዮች መጠላያ ካምፕ፤ ዶሎ፣ ሶማሊያ ዳርቻ 09/19/2022
ፎቶ ፋይል፦ የተፈናቀያዮች መጠላያ ካምፕ፤ ዶሎ፣ ሶማሊያ ዳርቻ 09/19/2022

ሶማሊያ በበርካታ አሰርት ዓመታት ባልታየ ድርቅ በተጎዳችበት በአሁኑ ወቅት የሚሰጣት ሰብዓዊ ዕርዳታ ሊቀነስባት እንደሚችል የጠቆሙ የሃገሪቱ የዕርዳታ ሠራተኞች ጉዳዩ እንዳሳሰባቸው አስታወቁ።

የለጋሾች መሰላቸት እና በዓለም ዙሪያ ሰብዓዊ ዕርዳታ የሚያስፈልጋቸው በርካታ ቀውሶች ስላሉ ሶማሊያ የምታገኘው ሰብዓዊ ድጋፍ መጠን ሊቀንስባት እንደሚችል የረድኤት ሰራተኞቹ ሰግተዋል።

በቅርቡ የሶማሊያ መንግሥት እና የሰብዓዊ ረድዔት ድርጅቶች በዚህ እአአ 2023 በሶማሊያ 7 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዜጎችን ለመርዳት የሚውል 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ መማጸናቸው ይታወሳል።

በመጪው የመጸው ወቅት በቂ ዝናብ ካልጣለ እና የሰብዓዊ ረድዔት ድጋፉ ካልቀጠለ ከባድ ቸነፈር ሊከሰት ይችላል የሚል ሥጋት አሰምተዋል።

ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG