በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ረሃብ በአፍሪካ

የቦረና ድርቅ ተጎጂዎች አስቸኳይ ድጋፍ እንዲደረግላቸው ጠየቁ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:37 0:00

በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን የድርቅ ተጎጂዎችን ለመርዳት በልዩ ልዩ ግለሰቦች እና ተቋማት እየተደረገ የሚገኘውን የድጋፍ ማሰባሰብ ያደነቁት የድርቅ ተፈናቃዮች፣ እርዳታው በቶሎ እንዲደርስላቸው ጠይቀዋል።

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በበኩሉ፣ የተሰበሰበውን እርዳታ በፍጥነት የሚያደርስ ኮሚቴ ማቋቋሙን ገልጾ፣ ለዚኽም ጥናት ሲያካሒድ መቆየቱን አስታውቋል።

በአንጻሩ እርዳታ ፈላጊዎቹ፣ ችግራቸው ጊዜ የማይሰጥ በመኾኑ በአስቸኳይ እንዲደርስላቸው ጠይቀዋል።

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ፡፡

የቀንድ ከብቶቹ በድርቅ ምክንያት የሞቱበት አርብቶአደር፤ ከጎዴ ከተማ በ80 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው ሃርጉጉዶ ቀበሌ ኢትዮጵያ 08/07/2023
የቀንድ ከብቶቹ በድርቅ ምክንያት የሞቱበት አርብቶአደር፤ ከጎዴ ከተማ በ80 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው ሃርጉጉዶ ቀበሌ ኢትዮጵያ 08/07/2023

በአፍሪካ ቀንድ ለስድስተኛ ወቅት ዝናብ በቀረበት በዚህ ግዜ ከሶማሊያ፣ ኢትዮጵያ እና ኬንያ የተፈናቀሉና በውሃ በምግብና በደህንነት እጦት የሚሰቃዩ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ልመታደግ አስቸኳይ ዕርዳታ እንዲደረግ የመንግሥታቱ ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ጥሪ አድርጓል፡፡

3.3 ሚሊዮን ለሚሆኑ ስደተኞችና የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሕይወት አድን ዕርዳታ ለመሥጠት 137 ሚሊዮን ዶላር ያስፈልጋል ሲል ኮሚሽኑ ጥሪ አድርጓል፡፡

በሶማሊያ ለአሁኑ ረሃብ እንዳይክሰት ለማድረግ ቢቻልም፣ ለሕይወት አስጊ የሆነ የምግብና የውሃ እጥረት እንዳለ የስደተኞች ኮሚሽኑ ቃል አቀባይ ኦልጋ ሳራዶ ትናንት ጀኒቫ ላይ ተናግረዋል፡፡

ግጭትና ድርቅ አንድ ላይ መከሰታቸው ቀድሞውንም አደገኛ የነበረውን ሁኔታ አባብሶታል ያሉት ቃል አቀባይዋ፣ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ለደህንነታቸው እና ዕርዳታ ለማግኘት ሲሉ መኖሪያቸውን ጥለው ሸሽተዋል ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያና ሶማሊያ 1.7 ሚሊዮን የሚሆኑ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች መኖራቸውን ኮሚሽኑ ይገልጻል፡፡ በተጨማሪም 180 ሺህ የሚሆኑ ሰዎች ከሶማሊያና ከደቡብ ሱዳን ወደ ኢትዮጵያና ኬንያ መሸሻቸውን ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡

በሶማሊያ ብቻ 287 የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ይገኛሉ፡፡

ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG